image
image
image
image
image

የልደታ ክ/ከተማ ንግድ ጽ/ቤት በመሰረታዊ የፍጆታ ሸቀጦች አቅርቦትና ስርጭትን አሰመልክቶ ባሉ ችግሮችና መፍትሄዎቻቸው ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አካሄደ።

የካቲት 18, 2018
በውይይቱ ነዋሪዎች፣ የምክር ቤት አባላት ፣የክፍለ ከተማና የወረዳ ንግድ ባለሙያዎችና የመሰረታዊ ፍጆታ አቅራቢ ድርጅት ማኬባ ተወካዮች በተገኙበት ተካሂዷል። የጽ/ቤቱ ኃላፊ ዶ/ር ጥበቡ ደጀኔ እንደተናገሩት የውይይቱ ዓላማ በመሰረታዊ የፍጆታ ሸቀጦች በተለይም ስኳርና ዘይት ስርጭት ላይ ያሉ ችግሮችን በጋራ ለይቶ መፍትሄ በማስቀመጥ የሸማቹን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ነው ብለዋል። ዶ/ር ጥበቡ አክለውም የመሰረታዊ ፍጆታ ሸቀጦች ፍትሀዊ ተደራሽነት እንዲሰፍን በቅዳሜና እሁድ ገበያዎች አቅርቦትን የማሻሻል እና የቁጥጥር ስራውን የማጠናከር ስራ መሰራቱንም ገልፀዋል። የውይይቱ ተሳታፊዎች በበኩላቸው በምርቶች ስርጭትና አቅርቦት ላይ ያሉ ክፍተቶች ለመሙላት ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት መደረጉ ባህል ሆኖ ሊቀጥል ይገባል ሲሉ ተናግረዋል። ፈጣንና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት የ ልደታ ክ/ከተማ ኮሚንኬሽን ገፆችን ይከታተሉ !! http://linktr.ee/lidetacommunication1

መልዕክትዎን ይላኩ

ሌሎች ዜናዎች