image
image
image
image

የልደታ ክፍለ ከተማ ንግድ ጽ/ቤት በ14ቱም ገበያዎች የገና በዓል ባዛር አስጀመረ

ታህሳስ 28/4/18, 2018
በልደታ ክፍለ ከተማ መጪውን የገና በዓል ምክንያት በማድረግ የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርቶች በተመጣጣኝ ዋጋ ቀርበዋል። የዋጋ ንረትን ለመቀነስ በክፍለ ከተማው በሚገኙ ሁሉም የባዛርና ሰንበት ገበያዎች የግብርና እና የኢንዱስትሪ ምርቶች በተመጣጣኝ ዋጋ የቀረቡ ሲሆን፣ የክፍለ ከተማው የገበያ ማረጋጋት ግብረ ሀይል በምርት አቅርቦትና በዋጋ ቁጥጥር በስፋት እየሠሩ ይገኛል። የክ/ከተማችን ነዋሪዎች የተረጋጋና በቂ የምርት አቅርቦት እንዲያገኙ የሚያስችሉ ዝግጅቶች የተጠናቀቀ ሲሆን ለበዓሉ አስፈላጊ የሆኑ የግብርና እና የፋብሪካ ምርቶች በመንግስት የገበያ ማዕከላት፣ በቅዳሜና እሁድ ገበያዎች እንዲሁም ለበዓሉ በተዘጋጁ ባዛሮች በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲቀርቡ ዝግጅት ተደርጓል። በእነዚህ የገበያ ማዕከላት የዳልጋ ከብት፣ በግና ፍየል፣ ዶሮ፣ እንቁላል እንዲሁም ከምግብ ፍጆታዎች መካከል የሆኑት የዘይት ምርት፣ የሰብል ምርቶች፣ አትክልትና ፍራፍሬ ለበዓሉ ገበያ ቀርበዋል። የበዓሉ ግብይት ስኬታማ እንዲሆን የልደታ ክ/ከተማው አስተዳደር፣ የንግድ ጽ/ቤት፣ የኅብረት ሥራ ጽ/ቤት፣ የአርሶ አደርና ከተማ ግብርና ጽ/ቤት እንዲሁም የኢንዱስትሪ ልማት ጽ/ቤት በቅንጅት እየሰሩ ይገኛል። መጪውን የገና በዓል ምክንያት በማድረግ ለበዓሉ የሚያስፈልጉ ግብዓቶች በገበያዎች የቀረቡ ሲሆን፣ ኅብረተሰቡም በአቅራቢያው በሚገኙ ገበያዎች ምርቶቹን በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲሸምት አስተዳደሩ ጥሪ አቅርበዋል።

መልዕክትዎን ይላኩ

ሌሎች ዜናዎች