image
image
image
image
image

የልደታ ክ/ከተማ አስተዳደር የኑሮ ውድነትን ለማረጋጋት እና የነዋሪውን የኑሮ ጫና ለማቃለል ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እየሰራ ይገኛል።

ሀምሌ 7, 2018
በክ/ከተማችን በሁሉም ወረዳዎች እና በተመረጡ ቦታዎች ላይ 11 የቅዳሜና የእሁድ ገበያ መዳረሻዎች አቋቁሞ የመሰረታዊ ፍጆታ ምርቶች እና የፋብሪካ ምርቶች በስፋት እና በጥራት እንዲሁም በተመጣጣኝ ዋጋ ለነዋሪ በማቅረብ ህብረተሰቡን ተጠቃሚ እያደረገ ይገኛል። በነዚህ የቅዳሜና እሁድ ገበያ መዳረሻዎች ከአርሶ አደሩ በቀጥታ የሚቀርቡ ምርቶች እየቀረቡ ሲሆን የምርትቹ ዋጋም ተመጣጣኝ ነው። የልደታ ክ/ከተማ አስተዳደር ከ11 የቅደሜና የእሁድ ገበያ መዳረሻዎች በተጨማሪ በሸማች ማህበራት በኩልም በተለይ የፋብሪካ ምርት የሆኑ እንደ ስኳር፣ ዘይት እና ዱቄት የመሳሰሉ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ እያቀረበ ይገኛል። በዚህ አጋጣሚ የክ/ከተማው አስተዳደር ባቋቋማቸው እና በአቅራቢያችሁ በሚገኙ የእሁድ ገበያዎች እንዲሁም የሸማች ማህበራት በመቅረብ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ በመግዛት ከአላስፈላጊ ወጪ እንድትቆጠቡ ጥሪውን ያስተላልፋል።

መልዕክትዎን ይላኩ

ሌሎች ዜናዎች