image
image
image
image
image

የልደታ ክፍለ ከተማ ንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት በወቅታዊ የገቢ አሰባሰብ ዙሪያ ውይይት አካሄደ።

ሀምሌ 1, 2018
የአዲስ አበባ ከተማ ንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ወ/ሮ ዘሀራ መሀመድ በመድረኩ እንደገለፁ የንግድና ዘርፍ ማህበራት በኢኮኖሚያዊና ያለው ሚና ከፍተኛ ነው በማለት ከመንግስት ጎን በመሆን ያሉ ችግሮችን እየፈታን ለውጥና ውጤት ለማምጣት በጋራ እንሰራለን ብለዋል። ማህበሩ ንግድና ኢንቨስትመት እንዲስፋፋ ያበረከተው ሚና ቀላል አይደለም ያሉት ወ/ሮ ዘሀራ መሀመድ በንግዱ ዘርፍ ተወዳዳሪ በመሆን ነጋዴው በአንድ ተደራጅቶ ያለውን ሀሳብ በማንሳት የንግዱ ሰርፍ የተሻለ ቁመና እንዲኖረው ያስፈልጋል በማለት ገልፀዋል። የልደታ ክፍለ ከተማ ም/ስራ አስፈፃሚና ስራና ክህሎት ጽ/ቤት ሀላፊ ወ/ሮ ነፃነት ደረሳ እንደተናገሩት የነጋዴ ማህበረሰብ በምናከናውናቸው ሰው ተኮር ተግባር ላይ የራሳችሁን ሚና በመወጣት ለላፊነታችሁን ተወጥታችኋል በማለት መንግስት ለሚሰበስበውም ግብር ነጋዴው የሚጠበቅበትን በታማኝነት በተቀመጠለት ጊዜ ገደብ በመክፈል ሀላፊነታችሁን ልትጡ ይገባል ሲሉ ተናግረዋል። አገር ከናንተ የምትጠብቀው በርካታ ነገሮች አሉ ያሉት ሀላፊዋ ይህን ደግሞ በመነጋገር በመወያየት በክፍለ ከተማችን ላይ የተሻለ የንግድ ስርዓት እንዲኖር በጋራ እንሰራለን በማለት ገልፀዋል። የልደታ ክፍለ ከተማ ንግድ ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ተስፍነሽ በጋሻው እንደተናገሩት በክፍለ ከተማች የሚገኙ በ10ሩ ወረዳዎች ያሉንን ነጋዴዎች የምክር ቤቱ አባል በማድረግ መብታቸውንና ግዴታቸን በአግባቡ ተገንዝበው በአግባብ መንቀሳቀስ እንዲችሉ ይረዳቸዋል በማለት በሰው ተኮርና በኮሊደር ልማት ከተማችን ውብና ንፁህ እንድትሆን የነጋዴው ሚና ጉልህ ነው በማለት ገልፀዋል። ነጋዴው ማህበረሰብ ተገቢውን አገልግሎት በመስጠት ያላቸውን ሚና ከመወጣት አንፃር እየሰሩ ያሉት ተግባር የላቀ ነው በማለት ወ/ሮ ተስፋነሽ በጋሻው ገልፀዋል። የልደታ ክፍለ ከተማ ንግድና ዘርፍ ማህበር ሰብሳቢ አቶ ተስፋዬ አበበ ነጋዴው የሚጠበቅበትን ግብር ለመክፈል የሚያስችለውን ግንዛቤ በመፍጠር ያለበቸውን ግዴታ በቅድሚያ በመክፈል ሀላፊነችሁን ልትወጡ ይገባል በማለት ገልፀዋል። ነጋዴው የምክር ቤቱ አባል በመሆን መንግስት የሰጠውን መብትና ግዴታ በአግባቡ ሊጠቀም ይገባል ያሉት አቶ ተስፋዬ አበበ ነጋዴው በተሰጠው መብት ተጠቃሚ በማድረግ በፍታዊነት ልሰሩ ይገባል ሲሉ ተናግረዋል። የምክር ቤቱ ተሳታፊዎችም በንግዱ ዘርፍ የተጣለብንን ሀላፊነት በመወጣት የማህበረሰብን ፍላጎት ማሟላት ይገባል በማለት ከኛ የሚጠበቅብንን ግብርም በወቅቱ መክፈል ይገባል።

መልዕክትዎን ይላኩ

ሌሎች ዜናዎች